Views: 1
ካራት ሰኔ 20/2017 ዓ.ም (ሳኢቴ ቢሮ)
ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተካልኝ ጋሎ ለመላው የኮንሶ ማህበረሰብ እንኳን “ለኾራ ኣታ ኾንሶ” ክብረ – በዓል በሠላም አደረሳችሁ/አደረሰን መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የኮንሶ ህዝብ ታታሪነት አለም የመሰከረለት፣ የተፈጥሮ ገጸ በረከት፣ ባህላዊ ዕሴቶች፣ የሰዉ ሰራሽና የተፈጥሮ ቅርሶች ባለቤት ነው።
የህብረተሰቡ የስራ ታታሪነት፣ በተራራ፣ በእርከን ስራና በአምባ መንደራት ላይ የታዩ በእጅ የተሰሩ የማይመስሉ የምህንድስና ጥበብ እጅግ የሚደነቅና በአለም አቀፍ ደረጃም እንዲታወቅ ያደረገበት በዓል በመሆኑን በመልዕክታቸው ።
አቶ ተካልኝ በመልዕክታቸው በኮንሶ ማህበረሰብ ዘንድ “የአንድነታችንና የታታሪነታችን መገለጫ “በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ በመላው የኮንሶ ማህበረሰብ ዘንድ በልዩ ዝግጅትና ድምቀት ለሚከበረው ክብረ – በዓል እንኳን በሠላም አደረሳችሁ/አደረሰን ብለዋል።
በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ እና የማህበረሰቡ ባህላዊ እሴቶች ይበልጥ ጎልተው የሚወጡበት እንዲሆንም ከልብ ተመኝተዋል።
መልካም በዓል!!