Views: 2
መስክ ምልከታው የተካሄደው የካራት ክላስተር ተስፋ ብርሃን ህብረት “ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት” በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ጎን ለጎን ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹ የፕሮጀክቱን የአፈጻጸም ሁኔታ በአካል ተመልክተዋል።
በLEC ኢንጂነሪንግ እየተገነባ ያለው የካራት ክላስተር ማዕከል የክልል ቢሮዎች ሕንፃ ለክላስተሩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል ለማቅረብ ከሚያስችሉ መሠረተ ልማቶች መካከል አንዱ መሆኑ ተገልጿል።
በምልከታው ወቅት የፕሮጀክቱ የአፈጻጸም ደረጃ ከሌሎች ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ጋር ሲነጻጸር አንስተኛ መሆኑ ተጠቁሞ፣ ግንባታው በተያዘለት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት እንዲገባ የሥራው ፍጥነት እንዲጨምር አስፈላጊ መሆኑ ተመላክቷል።
በመስክ ምልከታው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤና የካራት ክላስተር ተስፋ ብርሃን ብልጽግና ህብረት ሰብሳቢ ክቡር አቶ ዳርጌ ዳሼ፣ የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ወይንቱ መልኩን፣የብልጽግና ፓርቲ ምክርቤት አባልና የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኜ ሂዶ፣ እንዲሁም የተለያዩ ቢሮዎች ምክትል ኃላፊዎችና የተስፋ ብርሃን ብልጽግና ህብረት አባላት ተሳትፈዋል።