Views: 0
ካራት፣ ጥር 06/2018 ዓ.ም (ኢቴ ቢሮ)
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ የብልጽግና ፓርቲ ኢኖቬሽን ቤተሰብ “ክልላዊ የተቋማት ሪፎርም ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ሀሳብ ወራዊ የቤተሰብ ውይይት አካሄደዋል።
የቢሮው ኢኖቬሽን ቤተሰብ ሰብሳቢ ህብረት አታራ (ዶ/ር) የውይይት ሰነድ ዓላማ የተሳለጡ ተቋማት መገንባት የሚያስችል የአመራሩና የአባሉ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ሚና ለሁለንተናዊ ለዉጥ ወሳኝነት ለማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል።
የተመዘገቡ አጓጊ ጅምር የልማት ውጤቶች እንድሰፉ እና ሁሉም ህዝብ በየደረጃው በልፋቱ ልክ ተጠቃሚ እንድሆን የፓርቲያችን አመራርና የአባላት የበኩሉን ድርሻ ልወጣ ይገባል ብለዋል።
ጠንካራ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት ሀብትን ለታለመለት ዓላማ ብቻ የሚያዉሉ ብክነትን ወሳኝ በሆነ መልኩ በመቀነስ ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በትግል ያከሰሙ ተቋማት መገንባት እንደሚገባም ዶ/ር ህብረት አስገንዝበዋል።
የፓርቲው መደበኛ፣ ልዩ እና የህንፃ ግንባታ መዋጮዎች ለፓርቲው ዓላማ ስኬት መሠረታዊ በመሆናቸው ሁሉም አባላት የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
በውይይቱ መድረክ ከአባላቱ በተነሱ ጥያቄና አስተያየት ዙሪያ የቤተሰቡ ስብሳቢ ህብረት አታራ (ዳ/ር) ምልሽና ማብራሪያ በመሰጠት የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል።