የካራት ማዕከል ተስፋብርሃን የብልጽግና ኅብረት የ3ኛ ሩብ ዓመት የአባላት ኮንፈረንስ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል፣

Views: 0

ካራት፣ ሚያዚያ 29/2017 ዓ.ም

‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የካራት ማዕከል ተስፋብርሃን የብልጽግና ኅብረት የ3ኛ ሩብ ዓመት የአባላት ኮንፈረንስ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

‎በመድረኩም የኅበረቱ ሰብሳቢ አቶ ዳርጌ ባሼ በካራት ማዕከሉ ለሚገኘው አመራሮችና አባላት ለውይይት የ3ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም ሰነድ እየቀረበ ይገኛል።

‎በመድረኩ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳዬ፣ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተካልኝ ጋሎ፣ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወይኒቱ መልኩ እና የካራት ማዕከል የብልጽግና ኅብረት አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *