dr bogale

በሳይንስና ቴክኖሎጂ የበቁ አመራሮችን በመፍጠር ሀገራዊ ኢኒሼቲቦችን ውጤታማ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ

Views: 0

ቢሮው በሳይንስና ቴክኖሎጂ እና ስታርት አፕ ፓሊሲ ዙሪያ ለማኔጅመንት አካላትና ከፍተኛ ባለሙያዎች በአርባምንጭ ስልጠና ሰጥቷል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ (ዶ/ር)፤ መንግስት በ2030 ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት የያዘዉ ዉጥን እንዲሳካ በየደረጃው ያሉ የዘርፉ አመራሮች በከፍተኛ ኃላፊነት መስራት እንዲችሉ ስልጠናው ያግበዛል ብለዋል።

‎ቢሮው ሀገራዊ ኢንሼቲቦች በክልሉ ውጤታማ እንዲሆኑ ተልዕኮ እንደተሰጠውና ይህንንም ለማሳካት በሳይንስና ቴክኖሎጂው ዘርፍ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ዶ/ር ቦጋለ ጠቁመዋል።

ተቋማት አገልግሎታቸውን በቴክኖሎጂ በመደገፍና ዲጂታይዝ በማድረግ ቀልጣፋ፣ ፈጣንና እንግልትን በሚያስቀር መልኩ መፈፀም እንዲችሉ የማዘመን ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

‎በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዘርፍ ካውንስሎች እና ክልሎች ጉዳይ ኃላፊ አቶ ኑርልኝ ኮኩ፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ብቁ የሆኑ አመራሮችን ለመፍጠር በማሰብ ስልጠናው እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።

‎አክለውም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በአገሪቱ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የምርምርና የስርፀት ስራዎችን በመስራት በዘርፉ ተጨባጭ ለውጦች እንዲመዘገቡ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

‎በስልጠናው ዙሪያ የተለያዩ ሀሳቦችና የማብራሪያ ጥያቄዎች የተሰነዘሩ ሲሆን ከሚመለከታቸው አካላትና ከመድረኩ ሰፊ ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።

‎ስልጠናው በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ስታርት አፕ ፓሊሲ ዙሪያ ትኩረት ማድረጉን እና በቀጣይም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዙሪያ ለሚያከናውኑት ተግባር አጋዥ መሆኑን ሰልጣኞቹ ጠቁመዋል።

‎source:- South Television and radio Agency

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *